ጥያቄ(51): ሙስሊሞ የመርየም ልጅ የሆነውን ዒሳን አስመልክቶ ያላቸው ዐቂዳ (እምነት) ምንድነው? ተገድሏል ተሰቅሏል ማለትስ በሸሪዓው ያለው ብይን ምንድነው?
መልስ:
ሙስሊሞች የመርየም ልጅ የሆነውን ዒሳን አስመልክቶ ያላቸው እምነት፤ ባለሟል ከሆኑ መልክተኞች አንዱ ነው እንዲያውም ኡሉል ዐዝም (መካራን እና ችግርን በትግስት ተወጡ) ከሚባሉት አምስት ምርጥ ነብያት መካከል አንዱ ነው። አላህ በቁርኣኑ ሁለት ቦታዎች ላይ ጠቅሷቸዋል። ሱረቱ አሕዛብ ላይ እንዲህ ይላል፦
ሱረቱ አሹራ ላይ ደግሞ እንዲህ ይላል።
ዒሳ ያለ አባት ከእናት ብቻ የተፈጠረ የአደም ልጅ እና ሰብዓዊ ፍጡር ነው። እርሱም የአላህ ባሪያና መልክተኛ ነው። የማይመለክ ባሪያ ሲሆን ሊያስተባብሉት የማይገባ ነብይ ነው። የፈጣሪነትና የጌትነት መለያ አንዱም የለውም። እንዲያውም እርሱ አላህ እንዳለው ነው፦
እርሱንም ሆነ እናቱን ከአላህ ውጭ ያሉ አምላኮች አድርገው እንዲይዙ ህዝቦቹን አላዘዘም። አላህ ያወደረለትን ብቻ ነው ያዘዛቸው።
ዒሳ የተፈጠረው ሁን በሚለው የአላህ ቃል ትዕዛዝ ነው። አላህ እንዳለው፦
በኢሳና በመልክተኛው ሙሐመድ (صلى الله عليه وسلم ) መካከል የተላከ መልክተኛ የለም። አላህ እንዳለው ፦
ዒሳ የአላህ ባሪያና መልዕክተኛው መሆኑ ሳያምን አንድ አማኝ እምነቱ የተሟላ ሊሆን አይችልም። የሁዳዎች ዒሳን ከገለፁ አስፀያፊ ማንነት የፀዳ ነው። የሁዳዎች፦ እርሱ የዝሙተኛ ልጅ ነው አሉ።አላህ ይጠብቀንና እርሱ ከዝሙት ነው የተገኘው አሉ። አላህ ከዚህ ነጻ መሆኑን መስክሮለታል፤ሙስሊሞች እንዲሁ ክርስቲያኖች ከሚጓጓዙበት መንገድ የጠሩ ናቸው። እርሱና እናቱ ከአላህ ውጭ አምላክ አድርገው ስለያዙት። አንዳንዶቹ ደግሞ ፦ የአላህ ልጅ ነው በማለታቸው፤ ሌሎች ደግሞ የአላህ አንድ ሶስተኛው ነው (ስላሴን በማመናቸው)በማለታቸው ነው። ክርስቲያኖች የመርየም ልጅ የሆነውን ዒሳን ማንነት አስመልክቶ ግንዛቤያቸው የተሳሳተ ነው። ዒሳ ተገድሏል ወይም ተሰቅሏል የሚለውን አስመልክቶ አላህ በቁርኣኑ ይህ እንዳልተከሰተ በግልጽ እንዲህ ሲል አስቀምጦታል፦
ዒሳ ተገድሏል ወይም ተሰቅሏል የሚል እምነት ያለው ቁርኣንን በርግጥ አስተባብሏል። ቁርኣንን ያስተባበለ ደግሞ ካፊር ነው። ዒሳ አልተገደለም አልተሰቀለም ስንል እናምናለን። ነገርግን የሁዳዎች ተገድሏል ተሰቅሏል የሚለውን ውሸት በማራገባቸው የተነሳ ወንጀሉ እነሱ ተሸክሙት እንላለን። እርሱን ገደልነው ይላሉ እውነታው ግን አልገደሉትም አልሰቀሉትም። ነገርግን አምሳያውን ይዘው ገደሉት።ከነርሱ መካከልም የዒሳን መልክ አለበሰውና እርሱ መስሏቸው ይዘውት ሰቀሉት ገደሉትም። እኛ የአላህን መልክተኛ የመርየምን ልጅ አልመሲሕ ዒሳን ገደልን አሉ። ስለዚህም በአንደበታቸውም ሰቅለነዋል ገድለነዋል ብለው በማረጋገጣቸው የተነሳ ወንጀሉን የሁዳዎች ይሸከሟታል። ዒሳ ግን ከተባለው ነገር በሙሉ አላህ ነጻ አድርጎታል ከየሁዳዎች ሴራም ጠብቆ ወደ ሰማይ አሳርጎታል። የመጨረሻው ቀንም ሲቃረብ ወደ ምድር በመውረድ በነቢዩ ሙሐመድ (صلى الله عليه وسلم ) ሸሪዓ (ህግ) ያስተዳድራል ከዚያም የተወሰነለት ሞት አይቀርለትምና ይሞታል፤መሬት ውስጥ ይቀበራል። ሌሎች የሰው ልጆች ከቀብራቸው እንደሚቀሰቀሱት እሱም ዳግም ይቀሰቀሳል። አላህ እንዳለው፦
እንዲህ ብሏል፦