ጥያቄ(57): ከነዚህ ማለትም ከጠቀሷቸው አራት የተወሱል አይነት ውጭ ሌላ የተወሱል አይነት ይኖራልን?
መልስ:
አዎን። ከላይከጠቀስናቸው አራት የተወሱል ዓይነቶች ሌላ ተጨማሪ የተወሱል ዓይነት አለ። እርሱም፦ ዱዓው ተቀባይነት ይኖረዋል ተብሎ የሚከጀል ሰው ዱዓ ካደረገ በኋላ በሱ ዱዓ ወደ አላህ ተወሱል ማድረግ ነው። የነቢዩ ባልደረባዎች ለህዝባቸውም ሆነ ለግላቸው መልክተኛው ዱዓ እንዲያደርጉላቸው ይጠይቋቸው ነበር።
ቡኻሪና ሙስሊም ከአነስ ኢብኑ ማሊክ እንደዘገቡት “አንድሰ ሰው በጁምዓ ዕለት ነቢዩ ኹጥባ እያደረጉ ባሉበት ሰዓት ከፊት ለፊታቸው በኩል ባለው በር ገብቶ በመቆም እንዲህ አላቸው፦
ሰሓቦቹ ለግላቸው ነቢዩን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም ) ዱዓ እንዲያደርጉላቸው እንደጠየቁ የሚያሳዩ በርካታ ክስተቶች ይገኛሉ። ከነዚህም ክስተቶች መካከል የአላህ መልዕክተኛ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም ) ከኡመታቸው መካከል ሰባ ሺ ሰዎች ያለምንም ቅጣት ጀነት እንደሚገቡ ተናግረው ነበር እነሱም ሩቃ እንዲደርግላቸው የማይጠይቁ፣ጣጣቴ የማይጠቀሙ፣በገድ የማያምኑ እና በጌታቸው የሚመኩ ናቸው ብለው ሲናገሩ ዑካሻህ እብኑ ሚሕሰን “አንቱ የአላህ መልዕክተኛ ከነሱ እንዲያደርገኝ ዱዓ አድርጉልኝ፤አለ። እርሳቸውም ፦ “አንተ ከነሱ ነህ። አሉት”
ይህም ከሚፈቀዱ የተወሱል ዓይነቶች የሚመደብ ነው። ይኸውም አንድ ሰው ዱዓው ተቀባይነት ይኖረዋል ተብሎ የሚከጀልን ግለሰብ ዱዓ እንዲያደርገለት መጠየቅ ነው። ሆኖም ዱዓ እንዲደርግለት የሚጠይቀው ሰው እራሱን ብቻ በማሰብ ዱዓ መጠየቅ የለበትም ይልቁንም እርሱንም ሆነ ዱዓ አድራጊውን እንዲጠቅም በማሰብ ጥያቄውን ማቅረብ ይኖርበታል። ምክንያቱም እረስህንም ሆነ ወንድምህን መጥቀም የምትሻ ከሆነ ይህ ተግባርህ ከመልካም ተግባር ይቆጠራል።ስለዚህም ወንድሙም ወንድሙ በሌለበት እሱን አስቦ ዱዓ ካደረገ መላኢካው፦ “ ላንተም ለወንድም ባደረግከው ልክ ይሁንልህ።” ብሎ ዱዓ ያደርግለታል። በዚህም ተግባሩ ከመልካም ሰሪዎች ይመደባል። አላህ ደግሞ መልካም ሰሪዎች (አሳማሪዎችን) ይወዳል።