ጥያቄ(12): የሁለቱ የምስክር ቃላት ማለትም ላኢላህ ኢለሏህ ሙሐመዱ ረሱሉሏህ ትርጉም ምንድን ነው?
መልስ:
ሁለቱ የምስክር ቃላት ላኢላህ ኢለሏህ ሙሐመዱ ረሱሉሏህ ወደ ኢስላም መግቢያ ቁልፍ ናቸው። አንድ ሰው ወደ እስልምና መግባት ከፈለገ እነዚህን ሁለት ምስክር ቃሎች ካልሰጠ ወደ እስልምና መግባት አይችልም። ለዚህም ሲባል የአላህ መልክተኛው ሙዓዝን ወደ የመን በላኩት ግዜ የመጀመሪያ ጥሪውን ወደ ላኢላህኢለሏህ ሙሐመዱ ረሱሉሏህ እንዲያደርግ ነበር የመከሩት።
የመጀመሪያው የምስክር ቃል: ላኢላህ ኢለሏህ የሚለው የምስክር ቃል ሲሆን አንድ ግለሰብ በአንደበቱም ይሁን በቀልቡ ከአላህ በስተቀር የሚመለክ አምላክ እንደሌለ ማመን ይኖርበታል። “ኢላህ” ማለት የሚገዙት የሚያመልኩት ማለት ነው።
ላኢላህ ኢለሏህ የምትለው አ/ነገር ነፍይና ኢስባት በውስጧ ይዛለች። ነፍይ “ላ ኢላህ” የሚለው ሀረግ ውስጥ ሲሆን ኢስባት ደግሞ “ኢለ ሏህ” የሚለው ሀረግ ውስጥ ነው። ይህም ማለት ከአላህ በስተቀር በሐቅ የሚገዙት አምላክ የለም የሚለውን ትርጉም ይሰጠናል። መጀመሪያ በቀልብ ከአላህ በስተቀር በሐቅ የሚገዙት አምላክ የለም የሚለውን ካረጋገጠ በኋላ በአንደበት መመስከር ይገባል።ይህ ደግሞ አምልኮትን ለአላህ ብቻ በማጥራት ከርሱ ውጭ ካሉ አካል ውድቅ ማድረግ በውስጡ ይይዛል። ላኢላህ ኢለሏህ ስንል ምናልባት ከአላህ ውጭ የሚመለኩ ብዙ አማልክቶች አሉ አይደል ብሎ የሚጠይቅ ሰው ምላሽ ይሆን ዘንድ “በሐቅ የሚለው” በውስጠ ታዋቂ ማስቀመጣችንም ለዚሁኑ ነው እንለዋለን። አላህም በቁርኣኑ አማልክት በማለት ይጠራቸዋል አላህ በቁርኣኑ እንደሚለው፦
አላህ እራሱ ከርሱ ውጭ አማልክቶች መኖራቸውን እያረጋገጠ ከአላህ ውጭ የሚገዙት ሌላ አምላክ የለም እንዴት ይባላል? ከተባለ ለዚህ ምላሹ “ከአላህ ውጭ የሚገዙት ሌላ አምላክ የለም´ እነዚህ ከአላህ ውጭ የሚመለኩ አማልክቶች አዎን አማልክቶች ናቸው ነገር ግን የባጢል አማልክት እንጂ የሐቅ አማልክት አይደሉም። የአምልኮት መብት አንዱም አይገባቸውምና። ይህን የሚጠቁመው ቀጣዩ የቁርኣን አንቀፅ ነው።
የሚቀጥለውም አንቀፅ ይህኑ ይጠቁማል፦
አላህ ዩሱፍ ዐለይሂሰላም የተናገረውን አስመልክቶ እንዲህ ሲል በቁርኣን ላይ አስቀምጦታል፦
ስለዚህም ላኢላህ ኢለሏህ የሚለው ትርጉም ከአላህ በስተቀር በሐቅ የሚመለክ አምላክ የለም የሚለው ይሆናል።ከአላህ ውጭ ያሉ መልክተኞች፤መላኢካዎች፤ አውሊያዎች ድንጋዮች ዛፎች ፀሀይና ጨረቃ ለሎችም እነዚህ የሚያመልኩ ሰዎች አምላክ ናቸው ብለው ቢሞግቱም ትክክለኛ አምላክ ሳይሆኑ በባጢል የሚመለኩ አማልክት ናቸው። እንዲያውም ትክክለኛው የአምልኮ ተግባር ለአላህ ብቻና ብቻ ነው።